#እንድታውቁት

" ኢንፎኔት ኮሌጅ " ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞችን ሙሉ የትምህርት ማስረጃ እስከ ነሐሴ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንዲያስረክብ የአዲስ አበባ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳሰበ።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ፤ " ኢንፎኔት ኮሌጅ " በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በቴ/ሙ ዘርፍ እውቅና ፍቃድ በማግኘት ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱ ነገር ግን ኮሌጁ በባለስልጣኑ የእውቅና ፍቃድና እድሳት መመሪያ መሰረት ህጋዊ የቤት ኪራይ ውል ማቅረብ ባለመቻሉ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ #ፍቃድ_የሌለውና ፍቃዱም በባለስልጣን መ/ቤቱ #መሰረዙን ሚያዝያ 12/2014ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ እንዳሳወቀው አመልክቷል።

" ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ስልጠና እየሰጠ አለመሆኑን " በቀን 11/11/2015 ዓ.ም በተፃፈው ደብዳቤ ቁጥር ኢንፎ/2910/15 ገልፀውልናል " ያለው መ/ቤቱ  ኮሌጁ ቀደም ሲል እውቅና ፍቃድ በነበረው ወቅት ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞችን ሙሉ የትምህርት ማስረጃ እስከ ነሐሴ 17 / 2015 ዓ.ም ድረስ እንዲያስረክብ ቀነ ገደበ አስቀምጠናል ብሏል።

ኮሌጁ በተቀመጠው ጊዜ ይህን መፈፀም ካልቻለ በህግ ተጠያቂ እንደሚያደርገውም ባለስልጣን መ/ቤቱ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia