#Sudan

የጎረቤት ሱዳን ዜጎች በሰላም እጦት ሳቢያ የገዛ ሀገራቸውን ለቀው እየተሰደዱ ይገኛሉ።

ሱዳን አሁንም በጦርነት እየታመሰች ሲሆን ተዋጊዎቹ ኃይሎች ውጊያ የማቆም ፍላጎት እያሳዩ አይደለም።

በተደጋጋሚ በተለያዩ ሀገራት ጥረት የተኩስ አቁም እንዲደረግ እንዲሁም ዳጋሎ እና አል ቡርሃን ችግሩን እንዲፈቱ ጥረት ቢደረግም ውጤት አላስገኘም።

ዛሬም በርካቶች የሱዳን ዜጎች ሀገራቸውን ጥለው እየሸሹ ናቸው። የውጭ ሀገር ዜጎችም ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የሱዳንን ምድር እየለቀቁ ይገኛሉ።

በሱዳን ጦርነት ምክንያት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ በመተማ በኩል ፤ የ61 ሀገራት ዜጎች የሆኑ 7726 ሰዎች ገብተዋል።

@tikvahethiopia