TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሱዳን ውጊያ 6ኛ ቀኑን ይዟል።

በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል።

የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።

ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት እና የሱዳን ጦር ዋና መስሪያ ቤት አካባቢ ወታደራዊ ግጭት መኖሩ ተመላክቷል።

በርካቶች ያለምግብ፣ውሃ፣ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቤታቸው ውስጥ ዘግተው እንደተቀመጡ ይገኛሉ።

በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ቤታቸውን ጥለው ከካርቱም እየሸሹ እንደሚገኙ ተነግሯል።

@tikvahethiopia