TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ባጃጅ

• " ገደቡ ከነገ ጀምሮ ይነሳል "

• " በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይቻልም "


በአዲስ አበባ በባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ጀምሮ እንደሚነሳ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ዛሬ በሰጠው መግለጫ የባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 8/2015 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታውቋል።

የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ ቢሮው ገልጿል።

ቢሮው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚመራበት መመሪያ መዘጋጀቱን ይፋ ማድረጉን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

@tikvagethiopia