#EthioTelecom

የኢትዮጵያ መንግስት " ኢትዮ ቴሌኮም " ን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዛወር በድጋሚ ዓለም አቀፍ ጨረታ አወጣ።

አሁን የወጣው ጨረታ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ለዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ለማቅረብ ያለመ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ኩባንያዎች የማይመለስ 20 ሺህ ዶላር እና መተማመኛ በ13 ቀናት ውስጥ ማቅረብ እንደሚችሉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia