#DireDawa

3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ውጭ ተደርጎበት ተገንብቷል የተባለው የድሬዳዋ ደረቅ ወደብ እና ተርሚናል ዛሬ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ኢዜአ ዘግቧል።

የድሬደዋ ወደብ እና ተርሚናል በ34 ነጥብ 1ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን ባለሶስት ወለል የቢሮ ህንፃ ፣ መጋዘን ፣ የኮንቴይነር ተርሚናልና 10 ሄክታር የውስጥ ለውስጥ የኮንክሪት መንገድ አለው ተብሏል።

በተጨማሪም በአንድ ጊዜ 140 መኪናዎች ማቆም የሚያስችል የተገነባ ቦታ፤ ሁለት የዕቃ ማስቀመጫ መጋዘን እንዲሁም ወደቡን ከኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር የሚያገናኝ #የባቡር_ሃዲድ የተሰራለት እንደሆነ ተገልጿል።

Credit : ENA

@tikvahethiopia