TIKVAH-ETHIOPIA
" ወጣቶች እንዳይንቀሳቀሱ የማድረግ ዓላማ የለንም " - የትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን ፣ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ " የኢትዮጵያ መንግስት ሆነ የትግራይ ክልል ወጣቶች  #እንዳይንቀሳቀሱ_የማድረግ_አላማ_የላቸውም " ሲል የትግራይ ክልል የኮንስትራክሽን ፣ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቀ። ቢሮው ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጠው ቃል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀን እስከ 4 ጊዜ በረራ በማድረግ አገልግሎት…
#EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ #ከመቐለ በረራ ጋር በተያያዘ መግለጫ አውጥቶ ነበር።

ምን አለ ?

- ወደ መቐለ በረራ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ እና ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ መንገደኞችን እያገለገለ መሆኑን ገልጿል።

- አየር መንገዱ ቲኬት ገዝተው ወደ ቼክኢን ካውንተር የሚመጡ ተጓዦችን በአግባቡ እያስተናገደ መሆኑን አመልክቷል።

- የመቐለ በረራ በቀን አንድ ጊዜ የነበረ ሲሆን አሁን በየእለቱ የሚደረገው በረራ ወደ ሶስት ከፍ ማለቱን አሳውቋል።

- እለታዊ የበረራ ብዛት ቀንሷል የሚለው የተሳሳተ መረጃ ነው ብሏል፡፡ ወደፊትም የሚኖረውን የበረራ ፍላጎት እየታየ የበረራውን ብዛት ለመጨመር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

- #ከአዲስ_አበባ  ወደ  #መቐለ የሚጓዙ መንገደኞች የአየር መንገዱን የጥሪ ማእከል እና ቲኬት ቢሮዎች በመጠቀም ቲኬት መግዛት የሚችሉ ሲሆን ከመቐለ የሚነሱ ተጓዦች ደግሞ ከመቐለ የአውሮፕላ ማረፊያ የሽያጭ ቢሮ ቲኬቱን መግዛት ይችላሉ፡፡

በተጨማሪ ፦

የበረራ ቲኬቱን አ/አበባ በሚኖሩ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በኩል መግዛት የሚፈልጉ ደግሞ ቦሌ በሚገኘው " የኢትዮጵያ ኤርፖርት ኢንተርፕራይዝ ህንጻ " የምድር ወለል ከሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት እስከ ከሰአቱ 11፡00 ሰአት ድረስ መግዛት ይችላሉ ብሏል።

- አየር መንገዱ ባለፉት ስምንት ወራት የመቐለ በረራን ጨምሮ በሌሎች የሃገር ውስጥ በረራዎች ቲኬት ዋጋ ላይ ጭማሪ እንዳላደረገ ገልጿል።

- የኢትዮጵያ ዜግነት ላላቸው ተጓዦች እና የኢትዮጵያ የመኖሪያ ፈቃድ ላላቸው የውጭ ሃገር ዜጎች የመቐለ በረራ የቲኬት ዋጋ ለመሄጃ ብቻ ከ3450 ብር ጀምሮ ሲሆን፣ የደርሶ መልስ ቲኬት መነሻ ዋጋ ደግሞ 6895 ብር ነው፡፡ 

- " ሻንጣን " በተመለከተ #ከገና_በዓል ጋር ተያይዞ የተጓዦች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ በመጨመሩ የሻንጣ አገልግሎት ላይ መለስተኛ መጨናነቅ ተፈጥሯል።  በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ ተጨማሪ (ትርፍ) ሻንጣዎችን ለመቀበል ተቸግሮ ቆይቷል፡፡ አሁን ግን የካርጎ በረራ በመመደብ ችግሩን መፍታት ስለተቻለ ተጨማሪ ሻንጣ መቀበል ጀምሯል፡፡

Credit : Ethiopian Airlines

@tikvahethiopia