TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሕዝበ_ውሳኔ

በደቡብ ክልል ከሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ጋር በተያያዘ የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ብርቱካን ሚደቅሳ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

- የህዝበ ውሳኔ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ 2.9 ሚሊየን መራጮች ተመዝግበዋል።

- ቦርዱ ይህን ምርጫ ለማካሄድ የሚያግደው ምንም ነገር የለም ፤ አስፈላጊ ዝግጅቶች እንደተደረጉ ነው ብለዋል።

- የመራጮች ምዝገባ በዛሬው እለት የተጠናቀቀ ሲሆን መራጮች በ3,769 የመደበኛ፣ 11 የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አማካኝነት ተመዝግበዋል።

- የአሰራር ጥሰት የተፈጸመባቸው 24 ምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ነበር ፤ ጥሰቶቹ መራጮች ካርድ መሰጠት ለሌለባቸው ሰዎች ተሰጥቷል፣ ምርጫ ጣቢያ ያልተገኙ ሰዎች በመራጭነት ተመዝግበዋል፣ ከጣቢያ ውጪ ካርዶች ሲታደሉ ተገኝተዋል።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia