TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሕዳር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ብሏል። ሚኒስቴሩ ከአውሮፕላን ነዳጅ በስተቀር የነዳጅ ዋጋ #በጥቅምት_ወር በነበረው እንደሚቀጥል ገልጿል። የነዳጅ ዋጋው ከጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሕዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የሚዘልቅ ነው። በሁለተኛው ምዕራፍ ከመስከረም 18 ቀን 2015…
#ነዳጅ

ቤንዚን በሊትር 61 ብር ከ29 ሳንቲም ገባ።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ማድረጉን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ከዛሬ ታኅሣሥ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ በሚደረገው የዋጋ ክለሳ ዝቅተኛ ገቢ ላለው ሕብረተሰብ የሚሰጠው ድጎማ እንዲጨምር መደረጉንም ገልጿል።

በዚህም በአንድ ሊትር ቤንዚን ሲሰጥ የነበረው ድጎማ ከብር 15 ከ 76 ሳንቲም ወደ ብር 17 ከ 33 ሳንቲም እንዲሁም የአንድ ሊትር ናፍጣ ድጎማ ከብር 19 ከ02 ሳንቲም ወደ ብር 22 ከ 68 ከፍ እንዲል መደረጉ ተገልጿል።

በቀጣይ ፤ ሦስተኛ ዙር እና ከዛሬ ታኅሣሥ 30 ቀን 2015 ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆነው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ÷

- ቤንዚን በሊትር 61 ብር ከ29 ሳንቲም፣

- ነጭ ናፍጣ በሊትር 67 ብር ከ 30 ሳንቲም

- ኬሮሲን በሊትር 67 ብር ከ30 ሳንቲም

- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 49 ብር ከ67 ሳንቲም፣

- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 48 ብር ከ70 ሳንቲም እንዲሁም የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 67 ብር ከ91 ሳንቲም እንዲሸጥ ተወስኗል፡፡

ምንጭ፦ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ

@tikvahethiopia