TIKVAH-ETHIOPIA
20/80 እና 40/60 ውል ፦ የቤት እድለኞች #ውል_ለመዋዋል_ሲመጡ ማሟላት የሚጠበቅባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ምንድናቸው ? - እጣው የደረሰው ግለሰብ ውል ለመፈፀም በአካል መቅረብ፤ - በውጭ የሚኖሩ ጉዳያቸውን በውክልና ለማስጨረስ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ (አውታንቲኬት) ሆኖ የመጣ ውክልና ማቅረብ፤ - የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤ - የጋብቻ የምስክር ወረቀት ዋና…
#ማስታወሻ

ከነገ ከጥር 1 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለዕድለኞች ውል ማዋዋል ስራ ይጀመራል።

የውል መዋዋያው " #መገናኛ " በሚገኘው በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ ነው።

በሁለቱም የቤት ልማት መርሀ-ግብር ባለድለኞች #በአካል እየተገኙ ውል እንዲዋዋሉ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የውል ማዋዋሉ ፕሮግራም ለ60 የስራ ቀናት ወይም ለሁለት ወር ብቻ የሚቆይ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ተዋዋዬች ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በአንድ ማእከል የአገልግሎቱ መስጫ ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።

በተጨማሪ ቅድመ ሁኔታዎቹን በቢሮና በኮርፖሬሽኑ ዌብሳይት እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ማግኘት እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

በተሰጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ቀርቦ ያልተዋዋለ እድለኛ #በመመሪያ_ቁጥር 3.3/2011 መሰረት ቤቱን እንዳልፈለገው ተቆጥሮ ተመላሽ እንደሚደረግ ተገልጿል።

የቤት ባለ እድለኞች #ውል_ለመዋዋል_ሲሄዱ ማሟላት የሚጠበቅባቸው ቅድመ ሁኔታዎች በዚህ መመልከት ይቻላል 👇

https://publielectoral.lat/s/tikvahethiopia/75662

@tikvahethiopia