H. c. marketing directive draft 2nd edition (1) (1).pdf
142.6 KB
#Coffee : የውጭ ንግድ ደረጃ ያለውን ቡና በሃገር ውስጥ በውጭ ምንዛሬ ለመሸጥ የሚያስችል ረቂቅ የአፈጻጸም መመሪያ ይፋ ተደርጓል።

ይኸው መመሪያ ይፋ የተደረገው በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ሲሆን መመሪያው ለተጨማሪ ግብዓት ነው ይፋ የተደረገው።

ረቂቅ መመሪያው ከዛሬ ጀምሮ እስከ 15 ቀናት ድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተመልክተውት እና አስተያየት ከተሰጠበት በኋላ ሀሳቦቹ እንዲካተቱ ይደረጋል ተብሏል።

በረቂቅ መመሪያው ዙሪያ ማንኛውም አይነት አስተያየት ያለው ectacomm@gmail.com በሚለው ኢሜይል አድራሻ እስከ ጥር 9/2015 ዓ.ም ድረስ እንዲልክ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ጥሪ አቅርቧል።

(ረቂቅ መመሪያው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia