ፎቶ ፦ ጉምሩክ ኮሚሽን በኮምፒውተር " ሲስተም ዩኒት "  ውስጥ ተደብቀው የገቡ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች የኤሌክትሮኒከስ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገለፀ።

ኮሚሽኑ ፤ በሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ህጋዊ እቃዎችን ሽፋን በማድረግ በኮምፒውተር " ሲስተም ዩኒት " ውስጥ ተደብቀው የገቡ ፦

👉 100 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ፣
👉 ሀርዲስኮች
👉 ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ገልጿል።

ኮሚሽኑ ይፋ ባደረገው መረጃ ፦

- የኤክትሮኒክስ እቃዎቹ (ላፕቶፕ፣ ሀርድዲስክ፣...) የዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮችን ሲስተም ዩኒት ውስጡን ባዶ በማድረግ የገቡ ናቸው።

-  በተገኘ የፍተሻ ውጤት ሰነድ ላይ ያልተገለፀው ዕቃ የቀረጥና ታክስ መጠን ከ3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።

- የተፈፀመዉ #የንግድ_ማጭበርበር ተግባር  በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፤ ምርመራም እየተጣራበት ነው።

- በተያዘው እቃ ላይም የውርስ ውሳኔ ተሰጥቷል።

መረጃው ከጉምሩክ ኮሚሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia