TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #EU #UNICEF የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ31.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አደረገ። ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ የተቋረጡ የጤና አገልግሎቶች እንደገና እንዲጀምሩ ለማድረግ የአውሮፓ ህብረት (EU) የ31.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉን ያደረገው የማስጀመር እና የአቅም ግንባታ ስራ እንዲሰራ ለማስቻል ለተመድ የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) መሆኑን ኤፍ ቢ ሲ…
" የሰላም ስምምነቱን መደገፋችንን እንቀጥላለን " - አውሮፓ ህብረት

የአውሮፓ ህብረት የሰላም ስምምነቱን መደገፉን እንደሚቀጥል ዛሬ ባሰራጨው ፅሁፍ አረጋግጧል።

" ከሰላም ውጭ አማራጭ የለም " ያለው ህብረቱ አጋሮቹ UNICEF እና PLAN የህብረቱን የገንዘብ ድጋፍ በተግባር ላይ ማዋል ይጀምራሉ ሲል አመላክቷል።

የአውሮፓ ህብረት ፤ ለሕዝብ አፋጣኝ ቀጥተኛ ድጋፍ ለማረጋገጥ ሥራችንን እንቀጥላለን ብሏል። ህዝቡም የህብረቱን እንቅስቃሴ ይከታተል ዘንድ ጥሪ አቅርቧል።

ትላንት ህብረቱ የኢትዮጵያን ህዝብ #በቀጥታ እንደሚረዳ ገልጾ የትምህርት እና ጤና ዘርፉን ለመደገፍ 38 ሚሊዮን ዩሮ ( 2.1 ቢሊዮን ብር) ለግሷል።

" ልጆች ወደ ትምህርት ቤት ይመለሳሉ " ኢትዮጵያውያን የጤና አገልግሎት ያገኛሉ። " ያለው ህብረቱ የአውሮፓ ዜጎች ከፕላን ኢንተርናሽናል (PLAN) ኢትዮጵያ እና ዩኒሴፍ (UNICE) ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ኢትዮጵያውያንን ይረዳሉ ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia