TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ድልድዩ የፈረሰው መሸከም ከሚችለው በላይ ተማሪ ወጥቶበት መሆኑን ገልጿል። ዩንቨርስቲው ይህ የገለፀው ባወጣው መግለጫ ነው። " ዛሬ ጥዋት የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከዋናው ግቢ ወደ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲሸጋገሩ ሁለቱን ግቢዎች የሚያገናኘው ድልድይ ላይ ድልድዩ መሸከም ከሚችለው አቅም በላይ ተማሪዎች ሲወጡበት በመውደቁ አደጋ አጋጥሟል " ብሏል ዩኒቨርስቲው። "…
#Hawassa

" የተማሪ ወላጆች ተረጋጉ " - የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተማሪ ወላጆች እንዲረጋጉ ጥሪ አቀረበ።

ዛሬ ጥዋት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ ምክንያት የተወሰኑ ተማሪዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ያለው ከተማ አስተዳደሩ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በጤና ተቋማት በልዩ ሁኔታ ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብሏል።

በመሆኑንም የተማሪ ወላጆች እንዲረጋጉ የከተማው አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia