ኢትዮ ቴሌኮም ምን አጋጠመው ?

ኢትዮ ቴሌኮም የአገልግሎት እክል አጋጥሞት እንደነበር አስታወቀ።

ኢትዮ ቴሌኮም በአንደኛው ዋና ጣቢያው (core site) ላይ ባጋጠመው የውስጥ የኃይል አቅርቦት ቴክኒካል ችግር ምክንያት በከፊል ደንበኞቹ ላይ የአገልግሎት መቆራረጥ ችግር አጋጥሞት እንደነበር ገልጿል።

ለተፈጠረው ችግር #ይቅርታ የጠየቀው ኢትዮ ቴሌኮም ችግሩ የተፈታ መሆኑን አሳውቋል።

ዛሬ በከሰዓት በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የቴሌኮም አገልግሎት የሚያገኙ የድርጅቱ የተለያዩ ደንበኞች ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ አለመስራት፣ ስልክ ለመደወል አለመቻል ፣ SMS ለመላክ አለመቻልን ጨምሮ ሙሉ የአገልግሎት እክል አጋጥሟቸው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቹ ለመረዳት ችሏል።

@tikvahethiopia