G4 U1-3.pdf
65.4 MB
መነጋገሪያ የሆነው የ4ኛ ክፍል መፅሀፍ ምንድነው ?

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የተዘጋጀው የ4ኛ ክፍል የሒሳብ መፅሀፍ መነጋገሪያ ሆኗል።

ይህ መፅሐፍ መነጋገሪያ ሊሆን የቻለው በውስጡ #ገፅ_18 ላይ " የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች #በቀጥታ ከግሪክ ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው" የሚል ሀሳብ ይዟል በመባሉ ነው።

ይህም ጉዳይ በርካታ ዜጎችን አስቆጥቷል።

መፅሀፉ ውስጥ ገብቷል የተባለው ሀሳብ የታየው በሶፍት ኮፒ በተሰራጨው የመፅሀፉ ቅጂ ላይ መሆኑን በርካታ ወላጆች ልከውልን ተመልክተነዋል።

መምህራንም በተመሳሳይ ደርሷቸው እንደነበር ገልፀውልናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ ት/ት ቢሮ የተገለፀው ሃሳብ "በመጽሐፉ ውስጥ የማይገኝና ሆነ ተብሎ የተሰራጨ የሀሰት መረጃ" ነው ብሎታል።

ይህም የተደረገው ሆን ብለው ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ውዥንበር ለመፍጠር በሚፈልጉ አካላት ነው ሲል ገልጿል።

አዲሱ መፅሀፍ ህትመቱ ተጠናቆ በሁሉም ት/ቤቶች እየተሰራጨ መሆኑን አሳውቋል።

ቢሮው በPDF ስለተሰራጨው መፅሀፍ ያለው ነገር/የሰጠው ማብራሪያ የለም።

በዚህ ጉዳይ ላይ ግልፅ ማብራሪያ የሚፈልጉ ጉዳዮች፦

1ኛ. የሶፍት ኮፒ መፅሀፉ በማን፣ እንዴት፣ መቼ ተዘጋጀ ? ስህተት መሆኑ ከታወቀ እንዴት ተሰራጨ ?

2ኛ. ለት/ቤቶች #ታትሞ የተሰራጨው መፅሀፍ ዝግጅቱ መቼ ተጀመረ፣ መቼ ታተመ፣ መቼ ተጠናቀቀ ?

ሶፍት ኮፒው በትክክል ከሚመለከተው አካላት ተልኮ ከሆነ እና ስህተት ካለው "ሀሰተኛ / ህዝብ ውዥንብር ውስጥ ለመክተት የፈለጉ አካላት" ከማለት ስህተት መሆኑን በመግለፅ ማረም አይቻልም ነበር ወይ ?

ይህ ጉዳይ በዚህ ደረጃ መነጋገሪያ የሆነው ሀገር የሚረከቡ ትንንሽ ልጆች ስለሚማሩበትና ነገ ስለ ሀገራቸው ምን እያወቁ ነው የሚያድጉት የሚለው ስለሚያሳስብ ነው።

@tikvahethiopia