#DireDawa
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለቀጣይ አምስት ወር በመኖሪያ ቤት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግም ሆነ ተከራዮችን ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ አሳልፏል።
ከተማ አስተዳደሩ ፤ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ እና አለአግባብ ከፍተኛ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑን በተለያየ መንገድ አረጋግጫለሁ ብሏል።
ይህን ተከትሎ ነው ለ 5 ወራት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግ ሆነ ከተከራዩት ቤት ማስወጣት እንደማይቻል ውሳኔ ያሳለፈው።
#ዶቼቨለ
@tikvahethiopia