#ፓስፖርት

የፓስፖርት አገልግሎት ክፍያዎችን በ " ቴሌ ብር " አማካኝነት መፈፀም እንዲቻል በኢትዮ ቴሌኮም እና በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መካከል ዛሬ ስምምነት ተፈፅሟል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሪት ፍሬህወት ታምሩ ፤ ስምምነቱ አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት፣ እድሳት ለመፈፀም እና ሲጠፋ ሌላ ለማውጣት አገልግሎት ሲፈልጉ በቴሌ ብር ክፍያ መፈፀም እንደሚያችል ገልፀዋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሙሉጌታ በበኩላቸእ አገልግሎቱ በቀን ከ1,500 እስከ 2,000 የሚጠጉ ደምበኞች የሚስተናገዱበት መሆኑን በመግለፅ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተደረገው ስምምነት አገልግሎቱን ለማግኘት የሚፈጠረውን መጨናነቅ ይቀንሰዋል የሚል እምነት እንዳላቸዉ መናገራቸው ኢትዮ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia