#ተርኪዬ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ከአንካራ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት በድርጅቱ የቱርክ ሪፐብሊክ የሀገሪቱን ስም ከ "ቱርክ" ወደ "ተርኪዬ" መቀየሩን ዛሬ አሳውቋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች ፤ ከቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜቭሉት ካቩሶግሉ ለዋና ፀሃፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተላከው ደብዳቤ ለሁሉም ጉዳዮች የሀገሪቱ ስም ከ "ቱርክ" ይልቅ "ተርኪዬ" የሚለው ሥራ ላይ እንዲውል ተጠይቋል።

ቃል አቀባዩ ፤ የአገሪቱ የስም ለውጥ ደብዳቤው ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል ብለዋል።

@tikvahethiopia