" የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት በሚያዚያ ወር 12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ተደርጓል " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ፤ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ባሻቀበበት በዚህ ወቅት መንግሥት በሚያዚያ ወር ብቻ የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ማድረጉ ገልጿል።

ይህን የተገለፀው ከቀናት በፊት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ስለ አዲሱ የታለመ የነዳጅ ድጎማና ዋጋ ማሻሻያ በተመለከተ ለሚዲያ አካላት በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።

እስከ ሚያዚያ ወር ማጠናቀቂያ ድረስ በአንድ ወር ብቻ ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ድጎማ መደረጉ ታውቋል።

ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. አንስቶ በጠቅላላው ባለፉት አሥር ወራት በመንግሥት የተደረገው የተመዘገበ የድጎማ መጠን ከ73.5 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ሪፖርተር ጋዜጣ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።

https://telegra.ph/Reporter-05-08

@tikvahethiopia