TIKVAH-ETHIOPIA
#OFC የኦሮሞ ፊዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛው መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል። በዚህ መግለጫ ላይ ፤ ባለፉት 3 ዓመታት በሀገራችን የተከሰቱ ለአያሌ ንፁሃን ህይወት መቀጠፍ፣ ለከፍተኛ ንብረት ውድመትና ፣ ለዜጎች ክብር ውርደት የዳረጉ የርስ በርስ ጦርነቶች ማዘናቸውን ገልፀዋል። ከጥቂት ወራት ወዲህ ለእርስ በእርስ ጦርነቶቹ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ መንግስት…
' ብሄራዊ ምክክር '

የኦሮሞ ፊዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያላካከተና ገልልተኛ እና ተዓማኒነት በሌላቸው አካላት የሚመራ ብሄራዊ ምክክር የሀገሪቱን ችግር ይፈታል ብለን አናምን ብለዋል።

ጉባኤተኞቹ የተሳካ የሆነ ብሄራዊ ምክክር እንዲደረግ ያስችላሉ ያሏቸውን ምክረ ሃሳቦችን በዝርዝር አቅርበዋል ፦

👉 በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ግጭት እንዲቆም በማድረግ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ፤

👉 ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች በተለይም ባአሁን ጊዜ በተለያዩ እስር ቤቶች ግፍ እየተፈፀመባቸው ያሉ የኦፌኮ እና ኦነግ አመራር አባላት ካለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፤

👉 መንግስት የእርስ በእርስ ጦርነቱ ላይ እየተሳተፉ ካሉ የታጠቁ ኃይሎች ጋር #ድርድር በመጀመር እና ግጭቶች እንዲቆሙ በማድረግ ፣ ያሉትን የህግ ማነቆዎችንም ሙሉ በሙሉ በማንሳት ብሄራዊ ምክክር ላይ እንዲሳተፉ ሊጋብዛቸው ይገባል፤

👉 የብሄራዊ ምክክሩ አዋጅ ሊዘጋጅ የሚገባው በጋራ ስምምነት ሆኖ ኮሚሽነሮችም ምክክሩ ላይ በሚሳተፉ አካላት ሊመረጡ ይገባል ብለዋል።

(የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ)

@tikvahethiopia