#AmharaRegion

በጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል ፤ ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ባለው እጅግ የከፋ ችግር በርካታ ህፃት እና እናቶች ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፤ ይሄ በተደጋጋሚ ተገልጿል።

በችግር ላይ ላሉት ወገኖች ድጋፍ እየተደረገ ቢሆንም ካለው የከፋ ሁኔታ አንፃር ምንም ነው።

የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለሴቶች እና ሕጻናት 3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የአይነት እና ለ300 እናቶች ደግሞ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሚኮ ዘግቧል።

እንዲሁም በክልሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እስካሁን 200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ቢያደርጉም ከተከሰተው ችግር ስፋት ጋር የሚጣጣም ሆኖ አልተገኘም።

ችግሩንም መፍታት አልተቻለም።

መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፣ ባለሃብቶች በችግር ላይ ለወደቁ ወገኖች አሁንም ድጋፋቸው አጠናክሮ እንዲቀጥሉ እና ሕጻናትን እና እናቶችን መታደግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ፎቶ ፦ አሚኮ

@tikvahethiopia