TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ፌስቡክን አገደች። ሩስያ በሀገሯ ውስጥ ፌስቡክ የተሰኘው የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት እንዳይሰጥ ሙሉ በሙሉ ዘግታዋለች። ሩስያ ከጥቅምት 2020 ጀምሮ ቢያንስ 26 በሚሆኑ የሩሲያ ሚዲያዎች እና የመረጃ ምንጮ ላይ መድልዎ መፈፀሙን ገልፃለች። በተጨማሪም በቅርብ ጊዜ ከክሬምሊን ጋር የተቆራኙ የሚዲያ ምንጮች RT Newsና Sputnik News በመላው አውሮፓ እንዲገደቡ መደረጉን አመልክታለች። ይህንንም…
#Instagram

ሩስያ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ኢንስታግራም እንደሚታገድ አስታወቀች።

በሜታ ኩባንያ ስር የሚተዳደረው ኢንስታግራም ከሰኞ ጀምሮ እንደሚታገድ ሩስያ ገልፃለች።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው ሜታ ከዩክሬን ጦርነት ጋር ተያያዞ በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ግጭት ቀስቃሽ ንግግሮች ‘ለተወሰነ ጊዜ’ እንደሚፈቀድ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ነው።

ሜታ በፌስቡክ እና ኢስታግራም ላይ " ሞት ለወራሪው ሩስያ፣ ሞት ለሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና ሞት ለቤላሩሱ ፕሬዝደንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ " የሚሉ ልጥፎች በበርካታ አገራት ፈቅዷል እነዚህም አርሜኒያ ፣ አዘርባጃን ፣ ኢስቶኒያ ፣ ጆርጂያ ፣ ሃንጋሪ ፣ ላቲቪያ ፣ ሊቱዌኒያ ፣ ፖላንድ ፣ ሮማኒያ፣ ሩሲያ፣ ስሎቫኪያ እና ዩክሬን ናቸው።

ነገር ግን ድርጅቱ ንፁሃንን ኢላማ የሚያደርጉ ግጭትን ቀስቃሽ ንግግሮች እንደማይፈቅድ ገልጿል።

ሩስያ ፤ " ሜታ በፌስቡክ እና ኢስታግራም በዜጎቼ ላይ የጥቃት ጥሪዎች እንዲለጠፉ መፍቀዱ ከዚህ በፊት ተደርጎ የማይታወቅ ነው " ያለች ሲሆን በኢስታግራም በሩስያውያን ላይ የኃይል ጥቃት እንዲፈፀሙ ጥሪዎች እየተዘዋወሩ ነው ብላለች።

ይህን ተከትሎ ከሰኞ ጀምሮ ኢስታግራም በምድሪቱ ላይ እንደሚታገድ አሳውቃለች።

በሀገሪቱ ያሉ የኢንስታግራም ተጠቃሚዎች ባላቸው 48 ሰዓታት ውስጥ ፎቶ እና ቪድዮዎቻቸውን ወደ ሌላ ማህበራዊ ሚዲያ እንዲያዘዋውሩ እንዲሁም ለጓደኞቻቸው፣ ለተከታዮቻቸው እንዲያሳውቁ መልዕክት ተላልፏል።

ሩስያ ከዚህ በፊት #ፌስቡክ የተሰኘውን የሜታ ኩባንያ አካል የሆነውን የማህበራዊ ሚዲያ ማገዷ ይታወሳል።

@tikvahethiopia