#USA #ETHIOPIA

የአሜሪካው ከፍተኛ ባለሥልጣን (ስማቸው ያልተገለፀ) ለጋዜጠኞች ምን አሉ ?

• የኢትዮጵያ መንግስት ከአሜሪካ የንግድ ልዑክ የተነሱትን ቅሬታዎች በተመለከተ ተጨማሪ " አዎንታዊ እና ገንቢ " ዕርምጃዎች የሚወስድ ከሆነ ኢትዮጵያ ከተጠቃሚነት የተሰረዘችበትን የ #AGOA ዕድል በተመለከተ የንግግር ሒደት ውስጥ ለመግባት ፈቃደኛ መሆኑን ገልፀዋል።

• ታኅሳስ 28 ቀን 2014 ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ንግግር ማድረጋቸው የተገለጸው የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያደረጉት " በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ " መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

• አዲሱ ተሿሚ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ መቼ ወደ ቀጣናው ለመጓዝ እንዳሰቡ አልታወቀም ፤ ነገር ግን ረዥም [ጊዜ] እንደማይሆን ተገልጿል።

• ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በስልክ ንግግር ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለቱ መሪዎች ንግግር ያደረጉት በፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ጥያቄ መሠረት መሆኑን ተናግረዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/USA-ETHIOPIA-01-12

Credit : Reporter Newspaper