3 ልጆችን የተገላገለችው እናት ...

በወላይታ ዞን በጠበላ የመጀመሪያ ሆስፒታል አንዲት እናት 3 ልጆችን ተገላገለች።

በሁምቦ ወረዳ የኮይሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወይዘሮ ብርቱካን ዳርጮ ሁለት ወንድ እና አንድ ሴት 3 ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።

የተወለዱ ልጆችም ሙሉ በሙሉ ጤነኛና ክብደታቸውም በጥሩ ሁኔታ እንዳለ ከሆስፒታሉ ማረጋገጥ ተችሏል።

እናቶች የቅድመ ወሊድ ክትትል በጤና ተቋማት ውስጥ እንዲያደርጉና የባለሙያዎችን ምክር በተገቢው ተግባራዊ እንዲያደርጉ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር መንግሥቱ ሙንኤ አሳስበዋል።

ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia