#UPDATE😷

የኮቪድ-19 ቀውስ ዓለም አቀፍ መረጃ ፦

🇮🇹 በጣልያን በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ ሲሆን በትላንትናው ዕለት 98,030 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ 148 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

🇫🇷 ፈረንሳይ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 208,000 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች። በሀገሪቱ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች በአስደንጋጭ ሁኔታ እየጨመረ ነው።

🇧🇦 ቦሲኒያ #የመጀመሪያውን የኦሚክሮን ልውጥ ቫይረስ ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። 10 ሰዎች በኦሚክሮን መያዛቸው ሲረጋገጥ ምናልባትም ብዙ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ ተብሎ ተሰግቷል።

🏴󠁧󠁢󠁳󠁣󠁴󠁿 የስኮትላንድ ጠ/ሚ ስኮት ሞሪሰን አስቸኳይ ብሄራዊ የካቢኔ ስብሰባ ጠርተዋል። በሀገሪቱ የኮቪድ-19 ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እተባባሰ ነው ተብሏል።

🇵🇱 ፖላንድ በ4ኛው የኮሮና ቫይረስ ማዕበል እየተፈተነች ሲሆን በ1 ቀን 794 ዜጎቿ እንደሞቱባት የሀገሪቱ ምክትል የጤና ሚኒስትር አሳውቀዋል።

🇪🇸 በስፔን በአንድ ቀን ብቻ 100,760 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ወረርሽኙ ከጀመረ አንስቶ በቀን ከ100,000 በላይ ኬዝ ሲመዘገብ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ ነው። ለወረርሽኙ በዚህ ደረጃ መጨመር የኦሚክሮን ዝርያ መስፋፋት አንዱ ምክንያት እንደሆነ ተነግሯል።

🇪🇹 በኢትዮጵያ ሀገራችን ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ 11,749 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

🇺🇸 CDC በአሜሪካ በሚቀጥሉት 4 ሳምንታት ከ44 ሺህ በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ሊሞቱ እንደሚችሉ ተንብይዋል።

🌍 በዓለም አቀፍ ደረጃ እኤአ ከታህሳስ 22 እስከ ታህሳስ 28 ድረስ ባሉት ቀናት በየዕለቱ በአማካኝ 935,863 ሰዎች በኮቪድ-19 ሲያዙ የነበረ ሲሆን በአጠቃላይ 6,550,000 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

@tikvahethiopia