#SituationReport

#Tigray #Amhara #Afar

የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ /UN OCHA/ ሪፖርት ፦

- ከጥር ወር ጀምሮ በትግራይ እና በአማራ ክልል 728 ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ ህጻናት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገናኙ ሲሆን ይህም ከጠቅላላው 9 በመቶውን ብቻ የሚወክል ነው ተብሏል።

- ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ድረስ በሰሜን ኢትዮጵያ በሶስቱ ክልሎች ከ1,000 የሚበልጡ ከፆታ ጥቃት በህይወት የተረፉ ሴቶች በጤና አገልግሎት ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል።

- 500,000 የሚገመቱ ህጻናት ላይ ትኩረት ያደረገ ሰፊ የአመጋገብ ዘመቻ ለማካሄድ ከ5,700 በላይ እሽጎች ቫይታሚን ኤ ወደ አፋር ተልኳል።

- ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት ሳምንት በአማራ ከ 560 ሺህ በላይ ሰዎች የምግብ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል ፤ በአፋር ከ88 ሺህ በላይ ሰዎች እንዲሁም በትግራይ ከ138 ሺህ በላይ ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል።

- በትግራይ ባለው የነዳጅ እጥረት ምክንያት አንዳንድ አጋሮች ከታህሳስ 10 ጀምሮ የምግብ አቅርቦትን አቁመዋል።

ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/

@tikvahethiopia