#SituationReport
#Tigray #Amhara #Afar
የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ /UN OCHA/ ሪፖርት ፦
- ከጥር ወር ጀምሮ በትግራይ እና በአማራ ክልል 728 ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ ህጻናት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገናኙ ሲሆን ይህም ከጠቅላላው 9 በመቶውን ብቻ የሚወክል ነው ተብሏል።
- ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ድረስ በሰሜን ኢትዮጵያ በሶስቱ ክልሎች ከ1,000 የሚበልጡ ከፆታ ጥቃት በህይወት የተረፉ ሴቶች በጤና አገልግሎት ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል።
- 500,000 የሚገመቱ ህጻናት ላይ ትኩረት ያደረገ ሰፊ የአመጋገብ ዘመቻ ለማካሄድ ከ5,700 በላይ እሽጎች ቫይታሚን ኤ ወደ አፋር ተልኳል።
- ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት ሳምንት በአማራ ከ 560 ሺህ በላይ ሰዎች የምግብ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል ፤ በአፋር ከ88 ሺህ በላይ ሰዎች እንዲሁም በትግራይ ከ138 ሺህ በላይ ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል።
- በትግራይ ባለው የነዳጅ እጥረት ምክንያት አንዳንድ አጋሮች ከታህሳስ 10 ጀምሮ የምግብ አቅርቦትን አቁመዋል።
ሙሉ ሪፖርት :
https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/@tikvahethiopia