TIKVAH-ETHIOPIA
#USA : አሜሪካ በድሮን ጥቃት በካቡል ለገደለቻቸው ንፁሃን አፍጋነስታውያን ዘመዶች ካሳ እከፍላለሁ ብላለች። ከጥቂት ወራት በፊት ካቡል የአሜሪካ ጦር በድሮን ጥቃት ንፁሃንን መገድሉ፤ በኃላ እርምጃው በስህተት የተፈፀመ እንደሆነ መግለፁ ፤ ይቅርታም መጠየቁ አይዘነጋም። በወቅቱ አሜሪካ ጨቅላ ህፃናትን ጨምሮ አጠቃላይ 10 ሰዎችን ነበር የገደለችው። አሜሪካ ለገደለችው 10 ሰዎች ዘመዶች የገንዘብ ካሳ…
" አደጋውን ያደረሱት የሠራዊቱ አባላት አይቀጡም " - ፔንታገን

ባለፈው ነሃሴ ወር በአፍጋኒስታን በአሜሪካ ድሮን ለተገደሉ 10 ሰላማዊ ሰዎች የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር፣ ፔንታገን አደጋውን ያደረሱትን የሠራዊቱን አባላት እንደማይቀጣ አስታወቀ፡፡

ከዚህ ውሳኔ የተደረሰው የመከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን ከሁለት የበላይ አዛዦች የቀረበላቸውን አስተያየት ካጸደቁ በኋላ መሆኑ ተነግሯል፡፡

የፔንታገን ቃል አቀባይ ጆርን ከርቢ ለቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደተናገሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ በጉዳይ ላይ ተጨማሪ የተጠያቂነት ምርመራ እንደማይፈቅዱ ማስታወቃቸውን ገልጸዋል፡፡

ፔንታገን ገለልተኛ መርማሪ መድቦ ሁኔታውን ካጣራ በኋላ እኤአ ነሀሴ 29 የተፈጸመው አደጋ “አስዛኝ ስህተት ነው” ብሏል፡፡

“ የተፈጸመው ስህተት የተሳሳተ መረጃን አምኖ ከመቀበል እንጂ ከንዝህላልነት ወንጀል የተከሰተ ነው ብሎ እንደማያምንም ” ፔንታገን አስታውቋል፡፡

በወቅቱ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ከሀሚድ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ 13 አሜሪካውያንን ጨምሮ 170 የአፍጋን ሰዎችን በገደለበት ማግስት በተካሄደ የድሮን ጥቃት ሰባት ህጻናትን ጨምሮ 10 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል፡፡ ~ ቪኦኤ

@tikvahethiopia