This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Video : የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ትላንት ለስራ ጉብኝት በሄዱበት ካንሳስ ከተማ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የቀድሞ ፕሬዜዳንት ትራምፕ ደጋፊዎች ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።

የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር የሚያካሂደውን እንቅስቃሴ አጥብቀው ተቃውመዋል።

ተቃዋሚዎቹ ፥ " የጆ ባይድን አስተዳደር ሽብርተኛውን የህወሃት ቡድን የመደገፍ እንቅስቃሴውን ሊያቆም ይገባል፣ የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ ለማጥፋት የሚያካሄደው ጣልቃ ገብነትም ሊቆም ይገባል #NoMore” ብለዋል።

በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ፣ ገለልተኛና ነጻ መንግስት አለን ጣልቃ ገብነቱ እንዲቆም እናሳስባለን ሲሉም የሰልፉ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

የትራምፕ ባንዲራ የያዙ ወደ ደርዘን የሚጠጉ ሰዎችም ተቃውሞ ያሰሙ ሲሆን ፤ በፕሬዚዳንት ባይደን በደቡብ ድንበር አያያዝ፣ አሜሪካ ከአፍጋኒስታን መውጣት እና በ COVID-19 የደህንነት ጥንቃቄዎች ጉዳይ ተቃውሞ አሰምተዋል።

Video Credit : KMBC

@tikvahethiopia