የኢትዮጵያ መከላከያ አርማውን ቀየረ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ከዚህ በፊት ሲጠቀምበት የነበረውን ተቋማዊ አርማ መቀየሩን የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ ብ/ጄ አስፋው ማመጫ አስተወቁ።

ጄነራል መኮንኑ ፣ ተቋሙ ከዚህ በፊት ሲጠቀምበት የነበረውን አርማ የቀየረው አዲስ ከፈጠረው አደረጃጀትና እየተገበረ ካለው ሪፎርም አኳያ ገላጭ ባለመሆኑ መሆኑን አብራርተዋል ፡፡

እንደ ብ/ጄ አስፋው ማመጫ ገለፃ ፣ ተቋሙ አዲስ ይፋ ያደረገው አርማ ከተቋሙ ተልዕኮና ባህርይ አንፃር ልዩ ልዩ ትርጓሜዎችን የያዘ ነው።

ምንጭ፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia