TIKVAH-ETHIOPIA
#Turkey : ቱርክ የአሜሪካንን ጨምሮ የ10 አገራት አምባሳደሮች አገሯን ለቀው እንዲወጡ አዘዘች። እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የቱርክ ፕሬዘዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ባስተላለፉት ውሳኔ የአሜሪካንን ጨምሮ የ10 የአውሮፓ አገራት አምባሳደሮች አንካራን ለቀው እንዲወጡ ተወስኗል። አምባሳደሮቹ እንዲባረሩ የተወሰነው በፈረንጆቹ 2016 ዓመት ከተካሄደው እና ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጀርባ እጁ…
#RecepTayyipErdoğan

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ የሰጡባቸው የ10 ሀገራት አምባሳደሮች ፦

🇩🇪 ጀርመን
🇺🇸 አሜሪካ
🇸🇪 ስውዲን
🇳🇴 ኖርዌይ
🇳🇱 ኔዘርላንድስ
🇩🇰 ዴንማርክ
🇳🇿 ኒው ዚላንድ
🇫🇷 ፈረንሳይ
🇨🇦 ካናዳ
🇫🇮 ፊላንድ ናቸው።

ትላንት ፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ኤስኪሴሃይር በተባለ ስፍራ ለተሰበሰቡ ሰዎች ባደረጉት ንግግር ላይ እንዲህ አሉ ፦

" አምባሳደሮቹ ወደ ቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመሄድ ትዕዛዝ ለመስጠት ሊደፍሩ አይገባም። ምን መደረግ እንዳለበት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴራችን አስፈላጊውን ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ።

እነዚህ 10 አምባሳደሮች በአንድ ላይ በአገሪቱ ውስጥ ተቀባይነት የሌላቸው /ፐርሶና ነን ግራታ/ ሊባሉ ይገባል።

በአስቸኳይም መፍትሄ ይደረግለታል"

@tikvahethiopia