#RecepTayyipErdoğan
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ የሰጡባቸው የ10 ሀገራት አምባሳደሮች ፦
🇩🇪 ጀርመን
🇺🇸 አሜሪካ
🇸🇪 ስውዲን
🇳🇴 ኖርዌይ
🇳🇱 ኔዘርላንድስ
🇩🇰 ዴንማርክ
🇳🇿 ኒው ዚላንድ
🇫🇷 ፈረንሳይ
🇨🇦 ካናዳ
🇫🇮 ፊላንድ ናቸው።
ትላንት ፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ኤስኪሴሃይር በተባለ ስፍራ ለተሰበሰቡ ሰዎች ባደረጉት ንግግር ላይ እንዲህ አሉ ፦
" አምባሳደሮቹ ወደ ቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመሄድ ትዕዛዝ ለመስጠት ሊደፍሩ አይገባም። ምን መደረግ እንዳለበት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴራችን አስፈላጊውን ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ።
እነዚህ 10 አምባሳደሮች በአንድ ላይ በአገሪቱ ውስጥ ተቀባይነት የሌላቸው /ፐርሶና ነን ግራታ/ ሊባሉ ይገባል።
በአስቸኳይም መፍትሄ ይደረግለታል"
@tikvahethiopia