#UNSC : ደቡብ ሱዳን " ጎክማቻር " የሚባለው አካባቢ ከተመደበው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ጥበቃ ኃይል ጋር በተያያዘ በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ ስላለው ሁኔታ ለተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ገልፃ ተደርጓል።

ገለፃውን ያደረጉት በድርጅቱ የፖለቲካና የሰላም ግንባታ ክፍል የአፍሪካ ጉዳይ ምክትል ዋና ፃሃፊው ናቸው።

እኤአ መስከረም 14 ቀን የአንድ ኢትዮጵያዊ 🇪🇹 ሰላም አስከባሪ ህይወት የጠፋበትን ጨምሮ በ " ጎክማቻር " በቅርብ ጊዜያት በሰላም አስከባሪዎች ላይ የተደቀኑት አደጋዎች በጥልቅ የሚያሰጓቸው ሆነው እንዳገኟቸው የፀጥታ ምክር ቤቱ አባላት ተናግረዋል።

የደቡብ ሱዳን መንግስት የሰላም አስከባሪውን ኃይል የተልኮ ስልጣን ያለእንቅፋት እንዲያከናውን የማስቻል ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚሉ እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎችን የምክር ቤት አባላት ማቅረባቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia