ለአካል ጉዳተኞች በአይነቱ ለመጀመርያ ጊዜ በተከታታይ ለሶስት ቀን ሲሰጥ የነበረው የፈጠራ አቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ከጥቅምት 1 እስከ 3/2014 በተከታታይ ለሶስት ቀን ለአካል ጉዳተኞች (PWD) እንደ አገር በፈጠራ ሥራዎች እንዲሰማሩ የሚያግዝ ሁሉን አቀፍ የፈጠራ ፖሊሲ እንዲኖራቸው ለገበያ የሚቀርቡ ክህሎቶችን እና የግል ብራንዲንግን ለፖሊሲ ተሟጋችነት ለማሳደግ የሚያስችል በአይነቱ የመጀመርያ የሆን ስልጠና በሀገር በቀል የፈጠራ ስራዎች (Indigenous Innovation -I2) የበጎ አድራጎት ድርጅት ከCIPE ጋር በመተባበር ተሰጥቷል።

በስልጠናው መጨረሻ ላይ የስልጠና ተሳታፊዎቹ ድርጅቶቹ በስልጠናው ቀጣይነት ላይ እንዲሰሩ እና በኢትዮጵያ የኢኖቬሽን የፖሊሲ ማሻሻያ አካል ጉዳተኞችን ያካተተ እንዲደረግ ለአካል ጉዳተኞች ፍትሃዊ ተሳትፎ በመሟገት አምባሳደር ለመሆን ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።

@tikvahethiopia