#AAU

አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2013 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ነገ ያከናውናል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮችና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 6 ሺህ 163 ተማሪዎች ነገ መስከረም 29/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።

ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 3 ሺ 604ቱ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚመረቁ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 2 ሺህ 559 ተማሪዎች የድህረ ምረቃ ተመራቂዎች ናቸው።

155 ተማሪዎች በሦሥተኛ ዲግሪ (PhD) የሚመረቁ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ዳይሬክተር ጥላሁን ተስፋዬ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

የምረቃ ስነ ስርዓቱ በሸገር ፓርክ የወዳጅነት አደባባይ እንደሚከናወን ታውቋል።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦች የትምህርት ተቋማትን ብቻ ትኩረት አድርጎ መረጃ የሚልክላችሁን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገፅ መቀላቀል ትችላላችሁ : https://publielectoral.lat/s/joinchat/RYD_4tbNBwRoKR2h

@tikvahuniversity @tikvahethiopia