TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ ስንዴ ፣ ዘይት ፣ ስኳር እና ሩዝ ከቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ። ፖስታ ፣ ማካሮኒ እና እንቁላል ደግሞ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንደተነሳላቸው የገንዘብ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። የቀረጥ እና የታክስ ማሻሻያው ላልተወሰነ ጊዜ እንደሚቆይ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ዛሬ በሰጡት መግለጫ…
በመሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ የተፈረገው የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ፦

የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ከፊስካል ፖሊሲ አኳያ መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦችን የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ በማዘጋጀት ከነሐሴ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ በሚከተሉት መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ እንዲደረግ ወስኗል።

• ስንዴ ከውጭ ሲገባ ከጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን፣
• የምግብ ዘይት ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ስኳር ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ሩዝ ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነጻ እንዲሆን
• ፓስታ እና ማኮረኒ ከውጭ ሲገባም ሆነ በአገር ውስጥ ግብይት ሲፈጸምበት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ እንዲሆን እንዲሁም
• የደሮ እንቁላል ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲሆን

ማሻሻው ተግባራዊ ሲደረግ መንግስት በብዙ ቢሊዮን የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ በተደረገ ጥናት ተረጋግጧል።

የዋጋ ንረት በታክስ ብቻ የሚፈለገውን የዋጋ መቀነስ ስለማያመጣ አቅርቦትን ለመጨመር መንግስት በከፍተኛ ወጪ በመግዛት በዝቅተኛ ዋጋ ለህብረተሰቡ ከሚያቀርባቸው ከነዚህ መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች በተጨማሪ በሌሎች አካላት የሚገባውን በማከል አቅርቦቱ በከፍተኛ ደረጃ ይጨምር ዘንድ ለስድስት ወር ተፈቅዶ የነበረው ያለውጭ ምንዛሬ ሸቀጦችን የማስገባት አስራር ለሌላ ተጨማሪ 6 ወራት እንዲራዘም ተደርጓል።

ከዚህ ተጨማሪም መንግስት የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጠር እና ገበያውን ለማረጋጋት ተጨማሪ የገንዘብ ፖሊሲን ጨምሮ ሌሎች የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይወስዳል።

#DrEyobTekalgn #MinistryofFinance

@tikvahethiopia