#Dessise

የደሴ ከተማ ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው ለመጡ ዜጎች ጊዜያዊ ማረፊያ አዘጋጅቷል።

1ኛ. ቅዳሜ ገበያ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የማረፊያ "ጣቢያ አንድ ":- ከወልድያ እና ከጉባላፍቶ አካባቢ የመጡ ተፈናቃዮች ማረፊያ።

2ኛ.ዳዉዶ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የማረፊያ "ጣቢያ ሁለት":- ከባላ፡ከራያ አላማጣ እና ከኮረም አካባቢ የመጡ ተፈናቃዮች ማረፊያ።

3ኛ. ካራጉቱ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የማረፊያ "ጣቢያ ሶስት" ከመርሳ እና ከሀብሩ ወረዳ አካባቢ የመጡ ተፈናቃዮች ማረፊያ።

4ኛ. አድስ ፋና 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ማረፊያ "ጣቢያ አራት" ቆቦ ከተማና ከራያ ቆቦ አካባቢ የመጡ ተፈናቃዮች ማረፊያ እንዲሆን ተወስኗል።

ከተማ አስተዳደሩ በክፍለ ከተማ እና በቀበሌ ደረጃ መላ ህዝቡ፣ አመራሩ፣ በጎፍቃደኛ ወጣቶች አስፈላጊውን ትብብር ሁሉ ለተፈናቃዮች እንደሚያደርጉላቸው እምነት እንዳለው ገልጿል።

ከወቅታዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ያለውን የተፈናቃይ ቁጥር በመገንዘብ ልዩ እገዛ ለማድረግ ከወዲሁ ፍቃደኝነታቸውን በመግለፅ ወደተግባር ለገቡት የከተማድ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ምስጋና ቀርቧል።

@tikvahethiopia