ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።
የደ/ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ13ኛው ዙር የ2013 ዓ/ም ተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት እያከናወነ ነው።
ዛሬ የመጀመሪያው ዙር ምርቃት (በዋናው ግቢ) ሲሆን ነገ ደግሞ በቡሬ ካምፓስ ተማሪዎች ይመረቃሉ።
በአጠቃላይ ምን ያህል ተማሪዎች ይመረቃሉ ?
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን በመደበኛው፣ በማታና በክረምት
• ሴት 1193
• ወንድ 2122 በድምሩ ከ3,315 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ
በሁለተኛ ዲግሪ ፦
• 143 ሴቶችና
• 254 ወንዶች በድምሩ 397 ተማሪዎችን በአጠቃላይ 3712 ምሩቃንን በዋናው ግቢ ሃዲስ አለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ እና ሃምሌ 18/2013 ዓ/ም በቡሬ ካምፓስ ይመረቃሉ።
ከዩኒቨርሲቲው በተገኘው መረጃ በዋናው ግቢ 2,905 ተማሪዎች ናቸው የሚመረቁት።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን :
@tikvahuniversity