የቦዴፓ ዕጩ ተወዳዳሪ ሞተው ተገኙ።

በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ምርጫ ክልል ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩት አቶ አይናድስ ሞላ ደንበሩ በግልገል በለስ ከተማ ሞተው መገኘታቸውን ፓርቲው በይፋዊ ፌስቡክ ገፁ አሳወቀ።

ከዚሁ ጋር በተገኛ ፓርቲው የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ዮሐንስ ተሰማ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 በሰጡት ቃል ፥ "አቶ አይናድስ ሞላ ትናንት ማታ በግልገል በለስ ከተማ ተገድለው ተገኝተዋል" ብለዋል።

አክለውም ፥ "እጅግ በጣም አዛሳኝና ልብ ሰባሪ ክስተት ነው፤ የአሟሟቱ ሁኔታ ገና እየተጣራ ይገኛል" ሲሉ ገልፀዋል። ፓርቲው ለድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች፣ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች መጽናናትን ይመኛልም ብለዋል።

መረጃው ከኢት ኤፍ ኤም ሬድዮ እና ከፓርቲው ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ የተውጣጣ ነው።

@tikvahethiopia