TIKVAH-ETHIOPIA
#ከፍተኛ_ጥንቃቄ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት፤ ጅዳ #ለኢትዮጵያውያን የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል። ለፅ/ቤቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ እየደረሱ ባሉት መረጃዎች መሠረት የሳዑዲ የፀጥታ አስጠባቂ አካላት ፦ - በጄዳ ፣ - መዲና ፣ - ጂዛን እና መካ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ዜጎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት ጉዳዩ እስኪጣራ ኢትዮጵያውያን…
#Update #SaudiArabia #Attention

"...የአካል ወይም ንብረት ጉዳት የደረሰባችሁ ዜጎች ያላችሁን ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽ\ቤቱ ማቅረብ ትችላላችሁ" - በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ

የሳዑዲ ዓረቢያ የፀጥታ ኃይሎች በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን ተከትሎ ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ማስተላለፉ ይታወቃል።

በዚህ ሂደት በተለይ ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ ኖሯቸው በህግ አስከባሪ አካላት ከመጠን ያለፈ ኃይል አጠቃቀም ምክንያት የአካል ወይም የንብረት ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ያላቸውን ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

አሁንም #ኢትዮጵያውያን ተገቢውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዲቀጥሉ የቆንስላ ጽ\ቤቱ በድጋሚ የጥንቃቄ መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethiopia