የሮይተርስ ምርመራ ሪፖርት :

ሮተርስ ዛሬ ይፋ ባደረገው የምርመራ ሪፖርቱ የማይካድራ ጭፍጨፋን የሕወሃት ኃይሎች እንደጀመሩት ገልጿል።

አማራ ተወላጆችን የጨፈጨፉት ሻምበል ካሳዬ መኻሪ የተባለ የሕወሃት አባል ያደራጃቸው ሚሊሻዎች እንደሆኑ ከምስክሮች አንደበት መስማቱን ሮይተርስ አሳውቋል።

ሚሊሻዎች እንዲሁም የከተማዋ ፖሊስ አባላት የአማራዎችን መኖሪያ ቀበሌዎች በመክበብ በገጀራ እና ጥይት በጅምላ እንደጨፈጨፉ ሪፖርቱ አብራርቷል፡፡

የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች እና መከላከያ ሠራዊት ወደ ከተማዋ የገቡት ከጭፍጨፋው በኋላ እንደሆነ ሪፖርቱ ይገልጿል።

የሮይተርስ ሪፖርት የአማራ ክልል ታጣቂዎች በትግራይ ተወላጆች ላይ የበቀል ርምጃ መውሰዳቸውን ጠቅሷል፡፡

የሮይተርስ የምርመራ ሪፖርት👇
https://www.reuters.com/investigates/special-report/ethiopia-conflict-expulsions/ #Wazema

@tikvahethiopia