ቻይና ለትግራይ ክልል የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች።

ቻይና ለትግራይ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና ለሌሎች የህክምና አገልግሎት የሚውል የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች።

ድጋፉን የቻይና ኤምባሲ የኢኮኖሚና የንግድ ካውንስለር ሊ ዩ ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አብርሃም በላይ አስረክበዋል።

ድጋፉ ፦

- ሰባት (7) የመተንፈሻ እገዛ የሚሰጡ መሳሪያዎች (ቬንትሌተሮች)፣
- 36 ሺህ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል (ማስክ)
- 1 ሺህ 500 የህክምና አልባሳትን
- የህክምና እርዳታ ለመስጠት የሚያስችሉ የህክምና መሳሪያዎችና ቁሳቁሶች ያካተተ ነው።

ድጋፉ ከቻይና መንግሥትና ከቻይና ኩባንያዎች የተሰባሰበ ነው። #ENA

@tikvahethiopia