ዶ/ር አሸብር ወ/ጊወርጊስ የአኖካ የዞን 5 ፕሬዝደንት ሆነው ተመረጡ።
11 አባል ሀገራት ያሉት የአፍሪካ የዞን 5 ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ለፕሬዝደንትነት ኢትዮጵያ እና ግብፅ ለመጨረሻው ምእራፍ ደርሰው #ኢትዮጵያ 7 ድምፅ በማግኘት የፕሬዝደንትነት ቦታውን ተረክባለች።
የኢትዮጵያ ተቀናቃኝ የነበረችው #ግብፅ 3 ድምፅ ማግኘቷ ታውቋል።
በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝደንት ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ የዞን 5 የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር ፕሬዝደንት ሆነው ተመርጠዋል።
ይህንም ተከትሎ ኢትዮጵያ በአኖካ (የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር) ላይ የስራ አስፈፃሚ አባልነት ቦታን ታገኛለች ተብሏል።
መረጃው የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ነው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT