የግብፁ ፕሬዜዳንት ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።
የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲ ሲ በሱዳን የነበራቸውን ጉብኝት አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
በሱዳን ቆይታቸው ከሱዳን ሉዓላዊ ሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ውይይት አድረገዋል ፤ በጋራም መግለጫ ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንት ሲ ሲ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ፦ ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ ሳይደረስ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት የምታደርግ ከሆነ የሁለቱን ሀገራት ህልውና አደጋ ላይ ይጥላል ሲሉ ተደምጠዋል።
ፕሬዘዳንቱ ከዚህ ቀደም ሱዳን ከአፍሪካ ህብረት (AU) በተጨማሪ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ፣ የአውሮፓ ህብረት (EU) እና አሜሪካ በግዱቡ ጉዳይ አደራዳሪ እንዲሆኑ ያቀረበችውን ሀሳብ ግብፅም ትደግፋለች ብለዋል።
Source : SUNA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia