የብሄራዊ ባንክ ማሳሰቢያ ፦

ብሔራዊ ባንክ በትግራይ ክልል የአሮጌ ብር ቅያሪ ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 10 ቀን 2013 ዓ.ም ባሉ ቀናት እንዲጠናቀቅ ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ አሳስቧል።

ኅብረተሰቡ የባንክ ቅርንጫፎች በተከፈተባቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በመሄድ ገንዘቡን እንዲቀይር ተብሏል።

ባንኮችም በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ዛሬ የብሄራዊ ባንክ እንዳለው በትግራይ ይቀየራል ተብሎ የሚታሰበው የአሮጌ የገንዘብ መጠን በአብዛኛው ተቀይሯል ፤ ያልተቀየረው ቀሪ ገንዘብም ጥቂት ነው ፤ ይህ እንዲጠናቀቅ ነው የጊዜ ገደብ ያስቀመጠው።

Source : ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia