TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ የካቲት 8 የነአቶ ጃዋር መሃመድ ጠበቆች በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ እስረኞች የህክምና ጉዳይ አስመልክቶ ጉዳዩን ለሚያየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቤቱታ አቅርበው ነበር። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎትም እነአቶ ጀዋር መሀመድ በግል ሀኪሞቻቸው እንዲሁም በፈለጉት የግል ህክምና ተቋም መታከም እንደሚችሉ አፅንኦት ሰጥቶ ትዕዛዝ አስተላልፏል። ከቀናት…
አቶ በቀለ ገርባ ዛሬ ወደሆስፒታል ሲወሰዱ ምን ተፈጠረ ?

"አባቴ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ አላውቅም" - ቦንቱ በቀለ

ትላንት የእነአቶ በቀለ ገርባ ጠበቆች በእስር ላይ የሚገኙትን የፖለቲከኞች የህክምና ጉዳይ አስመልክቶ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቤቱታ አቅርበው ነበር።

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎትም እነአቶ በቀለ ገርባ በግል ሀኪሞቻቸው እንዲሁም በፈለጉት የግል ህክምና ተቋም መታከም እንደሚችሉ አፅንኦት ሰጥቶ ትዕዛዝ አስተላልፎ ነበር።

በፍርድ ቤቱ የተሰጠው ትእዛዝ አቶ በቀለ፣ አቶ ጃዋር፣አቶ ሃምዛ፣ አቶ ደጀኔ አ/አ ሜክሲኮ አካባቢ ላንድማርክ ጄነራል ሆስፒታል በአጃቢ አስፈላጊውን ጥበቃ ተደርጎ ህክምና እንዲወሰዱ የሚል ነው።

ነገር ግን በዛሬው ዕለት አቶ በቀለ ገርባ ወደ "ላንድማርድ ጄነራል ሆስፒታል" እንደሚወሰዱ ከተነገራቸው እና ከማረሚያ ከወጡ በኃላ የአጃቢ መኪኖቹና እሳቸውን የያዘው አምቡላንስ ከመንገድ ላይ ወደጦር ኃይሎች ሆስፒታል እንደወሰዷቸው ልጃቸው ቦንቱ ተናግራለች።

https://telegra.ph/BekeleGerba-02-16