#UPDATE

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በ11 ቀበሌዎች የተከሰተዉና በሰብል ላይ ወድመት እያደረሰ ያለዉን የአንበጣ መንጋን ለመቆጣጠር ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ በአንድ ኤሊኮፕተር የኬሚካል መርጨት ስራ እየተሰራ ነዉ፡፡

በተለይም በአዳማ ቀበሌ ልዩ ስሙ "ሲዳ" በሚባል አካባቢ የአንበጣ መንጋዉ በስፋት ሰፍሮ በሚገኝበት ቦታ የኬሚካል ርጭቱ የተከናወነ ሲሆን ከኬሚካል ርጭቱ ጎን ለጎን ሰብሎችን በማጨድ የማንሳት ስራም እየተከናወነ ይገኛል።

የሰብል ማሰባሰብ ስራው እየተሰራ የሚገኘው ፦
- በወረዳውና በከተማ አስተዳደር ህዝብ ፣
- በአማራ ክልል ልዩ ሀይል አባላት ፣
- ከሀገረ ማሪያም፣ በረኸትና አንጎለላና ጠራ ወረዳዎች በመጡ ሰዎች ጭምር ነው።

#MenjarShenkoraWerda
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia