#ለአርሶ_አደሩ_እንድረስለት !

በወረባቦ ወረዳ ውስጥ የተከተሰው የአንበጣ መንጋ አርሶ አደሩ ደክሞ ለፍቶ ያፈራውን ሰብል ወደ ጎተራው ሳያስገባ አንበጣ መንጋው እያወደበት ይገኛል።

ይህንን የሰብል ጉዳትም ለመቀነስ በሰው ሃይል የኬሚካል ርጭት ፣ በባህላዊ መንገድ የመባረር እና በሂሊኮፍተር ኬሚካል ርጭት ቢደረግም የአንበጣ መንጋውን መቆጣጠር አልተቻለም።

በመሆኑም የሲቪክ ማህበራት የመንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ባለሀብቶች በአንበጣ መንጋው ሰብላቸው የወደመባቸው አርሶ አደሮች እንዲደግፉ የወረባቦ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሳዳም ሽመልስ ጠይቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia