አንጋፋው አርቲስት አሊ ቢራ ህመም አጋጥሞት በህክምና ላይ ይገኛል !

የ73 ዓመቱ አርቲስት አሊ ቢራ ላለፉት 2 ሳምንታት በአዲስ አበባ እና አዳማ ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች የህክምና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

አርቲስት አሊ ቢራ ስላለበት ሁኔታ ለBBC ተከታዩን ብሏል ፦

"በፊት ላይ በጣም አሞኝ ነበር። አሁን ግን ተሽሎኛል። አሁን ያለሁበት ሆስፒታል ጥሩ ክትትል እያደረጉልኝ ስለሆነ ፈጣሪ ይመስገን እየተሻለኝ ነው።

አንዳንድ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ስለ እኔ ሐሰተኛ ወሬ በማሰራጨት ሰዎችን እያስደነገጡ መሆኑን ሰምቻለሁ። ሰዎች የመረጃዎችን እውነትነት ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።"

አርቲስት አሊ ቢራ አሁኑ የውስጥ ደዌ ህክምና እየተደረገለት ሲሆን ከዚህ ቀደምም የልብ እና የስኳር በሽታዎች ታማሚ መሆኑን #ለBBC ተናግሯል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia