ችሎት!

በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረውና ሸሽቶ በሃምሌ 3 ቀን 2012 ዓ.ም አዳአ ድሬ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በቁጥጥር ስር የዋለው ከበደ ገመቹ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

በዛሬው ዕለት በነበረው ችሎት መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በተጠርጣሪው ላይ የሰራውን ምርመራ ስራ ገልጿል። እየተከናወኑ ላሉ ስራዎች ተጨማሪ ምርመራዎች 14 ቀን እንዲሰጠውም ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ተጠርጣሪው በአስተርጓሚ አስተያየት ካለው እንዲያቀርብ የተጠየቀ ቢሆንም ፥ ምንም አይነት አስተያየት እንደሌለው ምላሽ ሰጥቷል። ጉዳዩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱ ለተጨማሪ መርመራ ለፖሊስ 14 ቀን በመፍቀድ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለነሃሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

Via Tarik Adugan (FBC)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia