ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሠጠ ማሳሰቢያ!

ከጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ግድብ በታችኛው ተፋሰስ በደቡብ ኦሞ ዞን ስር ለምትገኙ የዳሰነች ፣ ሰላማጎ ፣ ኛንጋቶም ፣ ሀመር ፣ ኦሞራቴ ፣ ካንጋቶን ከተማ ነዋሪዎችና የኦሞ ስኳር ፋብሪካ እንዲሁም በመስኖ ልማት ላይ የተሰማራችሁ ባለኃብቶች በሙሉ ከሐምሌ 25 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የግድቡ ውሃ ሊለቀቅ ስለሚችል ከወዲሁ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳስቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia